top of page
Search

የህይወት መንገዴ

  • Writer: snigussie
    snigussie
  • Feb 10, 2022
  • 1 min read

እንደ ብዙሃኑ ወልጄ ከብጄ

የተፈጥሮን ጥሪ አድምጬ ፈቅጄ

አልኖርኩም በወጉ ኑሮዬን አቅጄ

ይልቅ እጓዛለሁ በቀለም ሰክሬ

ሱስ ሆኖብኝ እውቀት ይኳትናል እግሬ

እጆቼ ይደክማሉ ይናውዛል ቀልቤ

ይሰደዳል ልቤ ይዋኛል ሀሳቤ

በጥበብ መዓዛ ወደፊት ተስቤ

ስምግ አረፍዳለሁ ከብራና ከርቤ

እውላለሁ ሳስስ ስነጠቅ ወደላይ

ክንፍ አውጥቼ ስበር በደመና ሰማይ

ስፈትሽ የኖርኩት የዘመናት ቅኔ

በጥልቅ ትንታኔ በሀሳብ ምናኔ

በስጋ ድካሜ ለነፍሴ ስንቅ ሀሴት

ለህሊና እርካታ ለመንገዴ ስምረት

አንዳች ባገኝ ብዬ የሚያፀና ሕይወት

አልፎ ሂያጅ ደስታን የሚያዘልቅ በረከት

እድሜ እማይገድበው የማያረጅ እውነት

ቀለሙ የማይለቅ ደብዝዞ እማይጠፋ

ከነፍስ የሚዋደድ ሰፍሬ በጭልፋ

ከጠቢባን ባህር ጥቂት ከፈላስፋ

ለማቅናት ነው መንገድ የሚበጅን ተስፋ

 
 
 

Recent Posts

See All
ያለ እግዚአብሔር ምንም

አለሁ አንተ ክበር የሁሉ ፈጣሪ በቀጭን ክር ተስፋ ነገር አሳማሪ ባንተ ያምራል ቀኑ ሲመሽም ሲነጋ ያንተ ጣት የነካው አይጎድልም ከዋጋ

 
 
 

Comments


Post: Blog2_Post

Subscribe Form

Thanks for submitting!

+251911358904

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • LinkedIn
  • Facebook
  • Facebook

©2022 by SanQa. Proudly created with Wix.com

bottom of page